የአንድነት ለዲሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ ሰማንያ አመራር አባላት በፓርቲዉ የስራ አፈጻጸም የወደፊት የትግል አቅጣጫ በፓርቲዉ ጽፈት ቤት በዝግ ሌት እና ቀን መምከራችዉ ተነገረ።
በጀርመንኛ መጠርያዉ ሜንሽን ፊዮር ሜንሽን ማለት ሰዎች ለሰዎች የተባለዉ ግብረሰናይ ድርጅት መስራች የሆኑት የአዉስትርያዉ ተወላጅ እዉቁ የፊልም ተዋናይ ዶክተር ካርል ሃይንዝ በም ከሰላሳ አመት አገልግሎት በኋላ አስተዳደሩን ማስረከባቸዉ ተገለጠ።
በ 600 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ፤ በሰሜን ሸዋ፤ ደርባ በተባለ አካባቢ የተገነባው የስሚንቶ ኢንዱስትሪ ትናንት በጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ተመርቋል። ባለፉት 5 ዓመታት እጅግ በመጨመር በግናባታው ዘርፍ ላይ ብርቱ ተጽእኖ አሳድሮ የነበረውን የሲሚንቶ ዋጋ አዲሱ ኢንዱስትሪ ያረጋጋዋል
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባዔ፣(ኢ ሠ መ ጉ)የአፍሪቃ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በተካሄደበት ሰሞን፤ ከተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብት ጽ/ቤትና ፤ ከአፍሪቃ ኅብረት የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ጋር፤ በሰብአዊ መብትና በአህጉሩ መሰል ድርጅቶች ተግባር ላይ መወያያቱ ተነግሯል።
የኢትዮጵያ ምክር ቤት ዛሬ ሁለት ተጨማሪ የጸረ ሽብር ህግ አጸደቀ፤ የጠቅላይ ሚኒስትሩንም የስድስት ወር የሥራ ዘገባ አደመጠ። ወኪላችን በላከልን ዘገባ እንዳመለከተዉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ካቀረቡት የሥራ ዘገባ ይዘት ይልቅ፤ በአዲሱ የከተማ ቦታ የሊዝ አዋጅ፤
የዕለቱን ዝግጅት ለማዳመጥ 16:00 - 17:00 የሚለውን ማገናኛ ይጫኑ። የአንድ ሣምንቱ የስርጭት ኮሮጆም ለማድመጥ በሚለው ሊንክ ይገኛል። አስተያየታችሁ ዓቢይ ግምት የሚሰጠው ነው፤ በ +49-228-429-164995 ደውሉልን። በዕለቱ ዓቢይ ርዕስ ላይ በ+49 172 26 66 944 በSMS አስተያየት ላኩልን።
ባጠቃላይ በዝግጅታችን ላይ አስተያየታችሁን በኢሜይልም ልትልኩልን ትችላላችሁ።
amharic@dw.de