1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የግብፅ መንግሥት እና የሲና የፀጥታ ሁኔታ

ሐሙስ፣ ጥቅምት 20 2007

የግብፅ መንግሥት በሀገሩ ሙሥሊሞች አኳያ የሚከተለውን ፖሊሲ ካልቀየረ በስተቀር በሲና በረኃ የአክራሪዎች ጥቃት እየተጠናከረ ሊሄድ እንደሚችል የፖለቲካ ታዛቢዎች አስጠነቀቁ። እንደሚታወሰው ፣ አንድ አጥፍቶ ጠፊ በዚሁ አካባቢ

https://p.dw.com/p/1Debm
Reaktionen auf die ägyptische Pufferzone im Sinai an der Grenze zum Gaza-Streifen
ምስል DW/ Shawgy al Farra

ከአምስት ቀናት በፊት ባነጎደው ቦምብ ቢያንስ 30 የግብፅ ወታደሮችን ገድሎ፣ 30 አቁስሎዋል፣ ሌሎች ታጣቂዎች በአንድ የጦር ኃይሉ መቆጣጠሪያ ኬላም ላይ ተኩስ ከፍተው ሶስት ወታደሮችን ሕይወት አጥፍተዋል። ይህን ተከትሎ የግብፅ ፀጥታ ኃይል ባለሥልጣናትም አካባቢውን በተሳለ መንገድ ለመቆጣጠር አንድ ነፃ ቀጠና ለማቋቋም የወሰኑ ሲሆን፣ በዚሁ አካባቢ የሚገኙት መኖሪያ ቤቶችን ስለሚያፈራርሱ ግብፃውያኑ ነዋሪዎች መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ በትናንቱ ዕለት አዘዋል።

ኬርስተን ክኒፕ

ይልማ ኃይለሚካኤል

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ