የእሥራኤል ምርጫ ውጤት ፤ ሥጋትና ተስፋው
እሑድ፣ መጋቢት 13 2007ማስታወቂያ
ዐበይት ስብሰባዎችም ፣ ስምምነቶችም ተደርገዋል። ያም ሆኖ ግን ፣ ፍጥጫው፣ ግጭቱ ፣ የሰላም እጦቱ እንዳለ ነው። ለእሥራኤልና ለፍልስጤማውያን ውዝግብ ሰላም በመሻቱ ሂደት ፤ የእሥራኤል ጠ/ሚንስትር ይስሐቅ ራቢን ጭምር መስዋእት ቢሆኑም ፤ እስካሁን ሁለቱን ወገኖች ለዘላቂ ሰላም የሚያበቃ መፍትኄ አልተገኘም። ምዕራባውያን የእሥራኤል ወዳጅ መንግሥታት ጭምር የተስማሙበት ፣ በአጠቃላይ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያገኘው ከእሥራኤል ጎን ፤ የፍልስጤም መንግሥት እንዲቋቋም የሚለው የመፍትኄ ሐሳብ፣ አሁን እንደገና በተመረጡት የእሥራኤል ጠ/ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ በምርጫ ዋዜማ ላይ «አይሞከርም!» የሚል ቃል መሠንዘራቸው አላስደነገጠም ፤ አላሳሰበም አይባልም። ከዚህ በመነሣት ፣እሥራኤል፤ ፍልስጤማውን፤ ባጠቃላይ ምንጊዜም ሰላም እንደጠማው የሚገኘውን መካከለኛውን ምሥራቅ ምን ያጋጥመው ይሆን?
ተክሌ የኋላ
ማንተጋፍቶት ስለሺ