1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአፍሪቃዉያን ስደተኞች ጎርፍ በኢጣልያ

ሐሙስ፣ ሚያዝያ 2 2006

ከሊቢያ የባህር ዳርቻ በሜዲተራንያን ባህር በኩል በጀልባ ወደ ደቡባዊ ኢጣልያ ግዛቶች የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር መጨመሩ ተገለፀ።

https://p.dw.com/p/1BfxQ
Flüchtlinge in Italien März 2014
ምስል picture-alliance/AP Photo/Italian Coast guard

የኢጣልያ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ባህር ላይ ለአደጋ የተጋለጡ 4000 የጀልባ ስደተኞችን መታደጋቸዉን አስታዉቀዋል። ካለፈዉ ጥር ወር ወዲህ ከሰሜን እና ከመካከለኛዉ ምስራቅ አፍሪቃ ሃገራት የመጡ በርካታ ስደተኞች ጣልያን መግባታቸዉን የሃገሪቱ የሃገር ዉስጥ አስተዳደር ሚኒስቴር አስታዉቋል። እንደ ሚኒስቴር መሥርያ ቤቱ፤ የሜዲተራንያን ባህር አካባቢ የአየር ፀባይ የተስተካከለ በመሆኑም፤ ከአሁን በኋላም በርካታ አፍሪቃዉያን ስደተኞች ሜዲተራንያንን አቋርጠዉ ወደ አዉሮጳ ለመግባት ጥርት እንደሚያደርጉ ተገልጿል ፤ ዝርዝሩን ተክለዝጊ ገ/እግዚአብሄር ልኮልናል

ተክለዝጊ ገ/እግዚአብሄር
አዜብ ታደሰ
ኂሩት መለሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ