1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የአዉሮጳ ጥምር ጦር ምሥረታ እቅድ

ማክሰኞ፣ መጋቢት 1 2007

በሩስያና በአዉሮጳ ሕብረት መካከል ዉጥረት ባለበት በአሁኑ ወቅት የአውሮጳ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ዣን ክሎድ ዩንከር፣ አዉሮጳ አቀፍ ጦር ሠራዊት እንዲቋቋም ሐሳብ ማቅረባቸው በአዉሮጳ ሃገራት ፖለቲከኞች ዘንድ ከፍተኛ ዉይይትን ቀስቅሶአል።

https://p.dw.com/p/1EoDV

ዩንከር «ዲ ቬልት » ለተሰኘዉ ጋዜጣ ባለፈዉ ሳምንት መጨረሻ እንደገለፁት የሚመሰረተዉ ጥምር ጦር፤ ወድያዉ ለስምሪት የሚላክ ስይሆን፤ ለጋራና ደሕንነቱ ለተጠበቀ አዉሮጳ የዉስጥና የዉጭ ፖለቲካ የሚቆም፤ አዉሮጳ በዓለም ያላትን ኃላፊነት የሚያረጋገጥ ነዉ ብለዋል። የጀርመንዋ መከላከያ ሚኒስትር ኡርዙላ ፎን ደርላየን የዩንከርን ሐሳብ ሲደግፉ፤ እንግሊዝን ጨምሮ በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ፖለቲከኞች ሃሳቡን በጥርጣሪ ነዉ የተመለከቱት። በዚህ ዝግጅታችን የአውሮጳ ሕብረት ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ዛን ክሎድ ዩንከር አዉሮጳ አቀፍ ጥምር ጦር ምሥረታ እቅድን በተመለከተ የዶይቼ ቬለዉ ሲቨን ፖይለ ያቀረበዉን ዘገባ ይዘን ብራስልስ የሚገኘዉን ወኪላችንን ገበያዉ ንጉሴን አነጋግረን ቅንብር ይዘናል።