1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የተባባሰው የዩክሬን ቀውስ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 13 2006

ለችግሩ መባባስ ምዕራቡ ዓለም ተጠያቂ የሚያደርጋት ሩስያ በኬቭ መንግሥት ላይ ወቀሳዋን አጠናክራለች ። ሩስያ የዩክሬን መንግሥት መገንጠል ከዩክሬን እንገንጠል በሚሉ ኃይሎች ላይ ፣ያለፈው ሳምንቱን ስምምነት በመጣስ ኃይል እየተጠቀመች ነው ስትል እየከሰሰች ነው ።

https://p.dw.com/p/1BlnK
Krise in der Ostukraine
ምስል DW/A. Sawitzkiy


ባለፈው ሳምንት ጄኔቫ ስዊትዘርላንድ ውስጥ ሩስያ ዩክሬን አሜሪካንና የአውሮፓ ህብረት የደረሱበት ስምምነት የዩክሬንን ውጥረትያረግባል ተብሎ የተጣለበት ተስፋ እየደበዘዘ ሄዷል ። ስምምነቱ ምሥራቅ ዩክሬን ውስጥ በኃይል የተያዙት የመንግሥት ህንፃዎች እንዲለቀቁ መሣሪያ የታጠቁም ትጥቃቸውን እንዲፈቱ የሚጠይቅ ቢሆንም ይህ እስካሁን ተግባራዊ አልሆነም ። ለችግሩ መባባስ ምዕራቡ ዓለም ተጠያቂ የሚያደርጋት ሩስያ በኬቭ መንግሥት ላይ ወቀሳዋን አጠናክራለች ። ሩስያ የዩክሬን መንግሥት መገንጠል ከዩክሬን እንገንጠል በሚሉ ኃይሎች ላይ ፣ያለፈው ሳምንቱን ስምምነት በመጣስ ኃይል እየተጠቀመች ነው ስትል እየከሰሰች ነው ። በዚህ መካከል የዩናይትድ ስቴትሱ ምክትል ፕሬዝዳንት ጆባይደንዛሬኬቭገብተዋል ስለ ዩክሬን ወቅታዊ ሁኔታ የበርሊኑን ወኪላችንን ይላማ ኃይለ ሚካኤልን ስቱ ድዮ ከመግባቱቴ በፊት በስልክ አነጋግሬው ነበር ።

ይልማኃይለሚካኤል

ሂሩት መለሰ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ