1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

የሊቢያ ህገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚቴና ተግባሩ

ሰኞ፣ ሚያዝያ 13 2006

ህገ መንግሥቱን የሚያረቁት ተወካዮች በሃገሪቱ ስር እየሰደደ የሄደውን ፖለቲካዊና ጎሳዊ ግጭቶች በተለይ በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል የሚቀርበውን የተጠናከረ የራስ ገዝ አስተዳደር ጥያቄ ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚኖርባቸው ተመልክቷል ። ረቂቁ እንደተጠናቀቀ ለህዝበ ውሳኔ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል ።

https://p.dw.com/p/1Blmk
Parlament in Libyen
ምስል picture-alliance/dpa


የሊቢያ አዲስ ህገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚቴ ምሥራቅ ሊቢያ ውስጥ ትናንት ሥራውን ጀመረ ። ከቤንጋዚ በስተምሥራቅ በምትገኘው ባይዳ በተባለችው ከተማ የተሰበሰቡት 47 ቱ አባላት ከሊቢያ ልዩ ልዩ ክፍሎች የተወከሉ መሆናቸው ተዘግቧል ።ህገ መንግሥቱን የማርቀቁ ሂደት ከተጠበቀው በላይ ጊዜ እንደሚወሰድ ይገመታል ። ህገ መንግሥቱን የሚያረቁት ተወካዮች በሃገሪቱ ስር እየሰደደ የሄደውን ፖለቲካዊና ጎሳዊ ግጭቶች በተለይ በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል የሚቀርበውን የተጠናከረ የራስ ገዝ አስተዳደር ጥያቄ ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚኖርባቸው ተመልክቷል ። ረቂቁ እንደተጠናቀቀ ለህዝበ ውሳኔ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል ። የዶቼቬለው አንድሪያስ ጎርትሴቭስኪ ያዘጋጀውን ዘገባ ይልማ ኃይለ ሚካኤል አጠናቅሮታል ።
ይልማ ኃይለ ሚካኤል
ሂሩት መለሰ
ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ