1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኤቦላ እና የኤኮኖሚ ተፅእኖው

ማክሰኞ፣ ነሐሴ 20 2006

የኤቦላ ተኀዋሲ በንክኪ የሚተላለፍ በመሆኑ በሽታው በዋነኝነት በተስፋፋባቸው በላይቤሪያ ሴራልዮን ና ጊኒ የንግድ እንቅስቃሴ እንዲገታ አድርጓል ።

https://p.dw.com/p/1Cyqr
Liberia Ebola (Bildergalerie)
ምስል Zoom Dosso/AFP/Getty Images

በምዕራብ አፍሪቃ እየተስፋፋ የሄደው ኤቦላ በአጭር ጊዜ ካልተገታ የማህበራዊና የኤኮኖሚ ቀውስ በማስከተል በሽታው የተዛመተባቸውን ሃገራት መንግሥታት ከፍተና ችግር ውስጥ እንደሚጥል እየተገለፀ ነው ። የኤቦላ ተኀዋሲ በንክኪ የሚተላለፍ በመሆኑ በሽታው በዋነኝነት በተስፋፋባቸው በላይቤሪያ ሴራልዮን ና ጊኒ የንግድ እንቅስቃሴ እንዲገታ አድርጓል ። ሶስቱ ሃገራት ድንበራቸውን የዘጉ ሲሆን ወደ እነዚህ ሃገራት የሚደረጉ በረራዎችም ለጊዜው ቆመዋል ። ይህም የሃገራቱን የቱሪዝምና የንግድ ኢንዱስትሪ በእጅጉ አዳክሟል ።በማዕድን ማውጣትና በልዩ ልዩ የኤኮኖሚ ዘርፎች የተሠማሩ ኩባንያዎች ሠራተኞቻቸውን ማስወጣታቸው ወይም እንዳይገቡ ማድረጋቸው በሃገራቱ ኤኮኖሚ ላይ ጫና ፈጥሯል ።ገበያው ንጉሴ ከብራሰልስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል

ገበያው ንጉሴ

ኂሩት መለሰ

ነጋሽ መሐመድ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ