1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ኢጣልያ እና የስደተኞቹ ችግር

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 15 2006

ኢጣልያ ባለፉት 48 ሰዓታት ከ1,000 የሚበልጡ ስደተኞችን ማዳኗን የሀገሪቱ የባህር ኃይል ትናንት አስታውቋል። ከሰሜን አፍሪቃ ወደ አውሮPA ለመግባታ ሲሞክሩ የመስመጥ አደጋ የሚያሰጋቸውን ስደተኞች ለማዳን ባለፉት ጊዚያት አንዳንድ ድርጅቶች ተቋቁ መው እየተንቀሳቀሱ ነው።

https://p.dw.com/p/1BnTd
Italien Marine rettet Flüchtlinge aus Afrika
ምስል picture-alliance/ROPI

ይሁንና፣ ስደተኞቹን የማዳኑ ተግባር ከቀኝ ክንፍ ፓርቲዎች ብርቱ ወቀሳ ተፈራርቆበታል። ይኸው የማዳን ተግባር ግን ብዙ ወጪ የሚጠይቅ ነው በሚል አሁኑኑ እንዲቆም ጠይቀዋል። ብራስልስ የሚገኘው የስደተኞች መብት ተከራካሪ ድርጅት ስደተኞቹን የማዳኑ ተግባር መቋረጥ እንደማይገባው በማስታወቅ ፣ ስደተኞቹን የማዳኑ እና የመቀበሉ ተግባር የሚጠይቀውን ወጪ ኢጣልያ ብቻ ሳትሆን ሌሎችም አውሮጳውያት ሀገራት ሊካፈሉት እንደሚገባ አሳስቦዋል።

ገበያው ንጉሤ

አርያም ተክሌ

ሸዋዬ ለገሠ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ