1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ታዋቂው የጀርመን ደራሲ ኅልፈት

ማክሰኞ፣ ሚያዝያ 6 2007

ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው በ87 ዓመቱ ሰኞ ሚያዝያ አምስት ቀን፣2007ዓ.ም ነው። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ በጀርመን ስነ ጽሑፍ ላይ ጉልህ አሻራውን አሳርፏል። የዓለም ሎሬት ማዕረግ ሽልማትንም ተጎናጽፏል፤ ደራሲ ጉይንተር ግራስ። ይኽ ደራሲ በጀርመን የስነጽሑፍ ታሪክ እጅግ ከፍተኛ ድርሻ አለው፤ አወዛጋቢነቱም የዛኑ ያህል ነው።

https://p.dw.com/p/1F7aG
Neueröffnung Günter Grass-Haus Lübeck
ምስል picture-alliance/dpa/Gambarini

የዛሬ ሦስት ዓመት « መነገር ያለበት» ሲል SüddeutscheZeitung በተሰኘው ጋዜጣ ላይ በጀርመንኛ ያቀረበው ግጥም እጅግ ከፍተኛ ውዝግብ አስነስቶ ነበር። «በብዕር ቀለሜ ጠብታ ፍፃሜ፥ በስተርጅናው ዘመኔ፥ መነገር ያለበትን ለወገኔ» በማለት የእስራኤል እና የኢራን የኑክሌር ይዞታን በማነፃጸር ትችታዊ ስንኝ ቋጥሮ ነበር። በዚህ ጽሑፉ በወቅቱ «ጸረ-ሴማዊ» በሚል ከፍተኛ ነቀፌታ ደርሶበታል። ከዚህ ዓለም ከተለየ ዛሬ አንድ ቀን አስቆጥሯል። ስለ ደራሲ ጉይንተር ግራስ ሕይወት እና ኅልፈት ሜኽትሂልድ ሜስከር ያዘጋጀውን ይልማ ኃይለሚካኤል እንዲህ ያቀርበዋል።

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ ከታች የሚገኘውን የድምጽ ማጫወቻ ይጫኑ።


ሜኽትሂልድ ሜስከር /ይልማ ኃይለሚካኤል
ማንተጋፍቶት ስለሺ
አርያም ተክሌ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ