1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

በሳዉዲ የኢትዮጵያዉያን ችግርና መፍትሄዉ

እሑድ፣ ኅዳር 22 2006

ኢትዮጵያ በሳውዲ ካለ ይኖሩ የነበሩ ከ50,000 የሚበልጡ ዜጎችዋን ወደ ሀገራቸው መመለስዋን በያዝነዉ ሳምንት መጀመርያ ማስታወቁ ይታወቃል። የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ችግር ያጋጠማቸውን ዜጎቹን የመመለሱን ተግባር ሲጀምር ቁጥራቸው 10,000 ይሆናል ብሎ ገምቶ ነበር።

https://p.dw.com/p/1ARIw
Titel: Äthiopien - Demonstration in Paris Thema: Äthiopien - Protest gegen Saudi Arabiens Aktion gegen Einwanderer aus Äthiopien Autor/Copyright: Haimanot Tiruneh Torode (Paris Korri.) 21.11.2013 Schlagworte:Äthiopien, Demonstration, Addis Abeba, Saudi Arabien, Einwanderer, Paris
ምስል DW/H. T. Torode

ይሁንና፣ አሁንም በሳዉዲ ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸዉ ኢትዮጵያዉያን ቁጥራቸው በውል እንደማይታወቅ እና፤ ምናልባትም ቁጥሩ ከፍ ሊል እንደሚችል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በዚሁ በያዝነዉ ሳምንት ለዶይቸ ቬለ መግለፃቸዉ ይታወሳል። በሳዉዲ አረብያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን በፀጥታ ኃይላት ከፍተኛ እንግልት እንደደረሰባቸዉ እና አሁንም በዚሁ ችግር ዉስጥ ያሉ ዜጎች ጥቂት እንዳልሆኑም እየተነገረ ነዉ። የዕለቱ የእንወያይ ዝግጅት በሳዉዲ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያንን ላይ ስለደረሰዉ ችግር አጠቃላይ ገጽታ እና በወቅቱ ዜጎችን ለመርዳት እየተደረገ ስላለዉ እንቅስቃሴ ባልደረባዪ ጀፈር አሊ፤ ተወያዩችን ይዞ ሐሳብ አሰባስቦአል።

ጀፈር አሊ

አዜብ ታደሰ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ