በሳዉዲ የኢትዮጵያዉያን ችግርና መፍትሄዉ
እሑድ፣ ኅዳር 22 2006ማስታወቂያ
ይሁንና፣ አሁንም በሳዉዲ ሕጋዊ ፈቃድ የሌላቸዉ ኢትዮጵያዉያን ቁጥራቸው በውል እንደማይታወቅ እና፤ ምናልባትም ቁጥሩ ከፍ ሊል እንደሚችል የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በዚሁ በያዝነዉ ሳምንት ለዶይቸ ቬለ መግለፃቸዉ ይታወሳል። በሳዉዲ አረብያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን በፀጥታ ኃይላት ከፍተኛ እንግልት እንደደረሰባቸዉ እና አሁንም በዚሁ ችግር ዉስጥ ያሉ ዜጎች ጥቂት እንዳልሆኑም እየተነገረ ነዉ። የዕለቱ የእንወያይ ዝግጅት በሳዉዲ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያንን ላይ ስለደረሰዉ ችግር አጠቃላይ ገጽታ እና በወቅቱ ዜጎችን ለመርዳት እየተደረገ ስላለዉ እንቅስቃሴ ባልደረባዪ ጀፈር አሊ፤ ተወያዩችን ይዞ ሐሳብ አሰባስቦአል።
ጀፈር አሊ
አዜብ ታደሰ