በሶማሊያ የሽግግር መንግስት ፕሬዝዳንት ሸሪፍ ሼክ አህመድና በጠቅላይ ሚኒስትር ኦማር አብድረሺድ ሻርማርኬ መኃል የተፈጠረው አለመግባባት ተካሯል። ምናልባት ደካማው የሽግግር መንግስት ሊለይለት ይችላል ተብሏል።
ፕሬዝዳንት ሸሪፍ
ሸርማርኬ
«ግልጽ አይደለም። በሁለቱ መሪዎች መኃል የተፈጠረው ችግር መሰረታዊ ምክንያቱ ምን እንደሆነ በትክክል አይታወቅም። ግን አንዳንድ ምንጮች እንደሚሉት ሁለቱ መሪዎች በአደባባይ እርስ በእርስ መወራረፍ ከጀመሩ ቆይተዋል። የሶማሊያ ብጥብጥ ከቁጥጥር ውጪ መሆኑ፤ አንዱ አንደኛው ላይ ማላከክ፤ ጥፋተኛ አድርጎ መኮነንን ይዘዋል። ፕሬዝዳንቱ የሚሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሃገሪቱን ደህንነት ማስጠበቅ አልቻሉም። አቅሙም የላቸውም--ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደግሞ ፕሬዝዳንቱ ለቦታው የሚመጥኑ አይደሉም ይላሉ። እስካሁን ስለሁለቱ መሪዎቹ ችግር የተረዳነው ይህንን ነው።» መሳይ መኮንን ነጋሽ መሐመድ