የርዋንዳ መንግስት ከሙስና ነጻ በሆነበትና ከስምንት መቶ ሺህ የሚበልጡ ቱትሲዎች እና ለዘብተኛ ሁቱዎች የተገደሉበት የጎሳ ጭፍጨፋ ትቶት ካለፈው መዘዝ ማገገም በቻለበት ድርጊት የኤኮኖሚ ጠበብት እና ዲፕሎማቶች ያደንቃሉ።
የሩዋንዳዉ ፕሪዝደንት ፓዉል ካጋሜ
በአሁኑ ጊዜ የርዋንዳ ህዝብ ወጣት ትውልድ ይበዛዋል። አብዝኃኑ ከሰላሳ ዓመት በታች መሆኑን እና በሀገር ግንባታው ስራም ላይ ማለፊያ አስተዋጽዖ በማድረግ ላይ መሆኑን ካጋሜ ሰሞኑን በብሪታንያ ለሮያል ኮመንዌልዝ ማህበረሰብ ባሰሙት ንግግር ላይ ገልጸዋል።
አርያም ተክሌ/DW