በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች የመብት ረገጣ ብቻ ሳይሆኑ ጤናቸዉን የሚጎዱ መሆናቸዉ እየታወቀ ይመስላል።
ሴቶች ላይ የሚፈፀመዉ ግርዛት ከጊዜያዊ ስቃይና ህመምነቱ ባሻገር በወሊድና ተያያዥ ጉዳዮች ወቅት የሴቶችን ጤና ለችግር የሚዳርግመሆኑን ተገንዝበዉ እንዲቆም የሚታገሉ ወገኖች ቁጥር ከፍ እያለ ነዉ። ከዓመታት በፊት በከንባታ ጠንባሮ አካባቢ ይፈፀም የነበረዉ ይህ ድርጊት አሁን አላስፈላጊነቱን በተገነዘቡ ወገኖች የተቀናጀ ጥረት ቀንሶ ወደሶስት ከመቶ ወርዷል። በተመሳሳይ በትግራይ 50በመቶ ሲቀንስ ባጠቃላይ በአገር ደረጃ ደግሞ 25በመቶ መድረሱ ይነገራል።
ሸዋዬ ለገሠ
ነጋሽ መሐመድ