አርብቶ አደሮች ከብቶቻቸዉን ከቦታ ወደቦታ በማዘዋወር ኑሯቸዉን የሚገፉ የኅብረተሰብ ክፍሎች ናቸዉ። ከተፈጥሮ ጋ ያላቸዉ ቁርኝትም በግልፅ ያታያል።
አርብቶ አደሮች በቀብሪ ደሃር
የኑሯቸዉ መሠረት ለሆኑት ከብቶቻቸዉ ግጦሽና ዉሃ ፍለጋ ከአንድ ቦታ ወደሌላዉ ወቅቱን ተከትለዉ ሲዟዟሩ እግረ መንገዳቸዉን ታዲያ የአካባቢ ተፈጥሮን ያግዛሉ ይላሉ የአካባቢ ተፈጥሮ ተቆርቋሪዎች። በአንፃሩ ከከብቶች ፍግና እበት የሚወጣዉ ጋዝ አካባቢን ይበክላል፤ እንቅስቃሴያቸዉም እንዲሁ ችግር አለዉ የሚሉ ወገኖች ከቦታ ቦታ ከሚዟዟሩ ይልቅ በአንድ አካባቢ ረግተዉ ከከብቶቻቸዉ የሚያገኙትን ጥቅም በተሻለ ስልት ቢጠቀሙና ሌላዉንም ማኅበረሰብ ቢጠቅሙ እንደሚበጅ ይናገራሉ።
ሸዋዬ ለገሠ፤ ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
አርያም ተክሌ