በኢትዮጵያ ብቻ ከሚገኙት ዛፎች መካከል አንዱ የሆነው በሳይንሳዊ መጠሪያው ኮርዴዮ ኤዱሊስ፡ ሶማሌዎች ደግሞ የዕብ የሚሉት ዛፍ ካለፉት ጥቂት ጊዚያት ወዲህ በብዛት እየተቆረጠ ብርቱ የመጥፋት ስጋት ተደቅኖበታል።
ይኸው በሶማል ክልል በዋርዴ ዞን፡ ቡኽ ወረዳ የሚገኘው ብርቅየ ዛፍ ፍሬው በምግብነት፡ ቅጠሉ ለከብቶችና ለግመሎች በመኖነት፡ ግንዱ ደግሞ ለህንጻ ግንባታና ለማገዶ ያገለግላል። ከአስር ዓመታት በፊት በመቶ ካሬ ኪሎሜትር ላይ ይገኝ የነበረው የዕብ ዛፍ በአሁኑ ጊዜ በሀያ ሁለት ካሬ ኪሎሜትር ስፋት ላይ ብቻ እንደሚገኝ ተመራማሪዎች ገልጸዋል። ዩሀንስ ገብረእግዚአብሄር