የዓለም ዜና፦ ሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓ.ም.
የሚያዚያ 15 ቀን 2016 ዓም አርዕስተ ዜና የይገባኛል ጥያቄ በሚነሳባቸው በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች በሚገኙ ከተሞች በተነሳው ግጭት የተፈናቀሉት ሰዎች ቁጥር ከ50 ሺህ መብለጡን የተመድ አስታወቀ። ስደተኞችን የጫነች ጀልባ ጅቡቲ የባህር ዳርቻ ላይ ሰጥማ 16 ሰዎች መሞታቸውን 28 ሰዎች ደግሞ የደረሱበት እንዳልታወቀ IOM ዛሬ አስታወቀ። የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪቺ ሱናክ ብሪታንያ የሚገኙ ተገን ጠያቂዎችን ወደ ሩዋንዳ ከመላክ የሚያግዳቸው እንደሌለ አስታወቁ። ስደተኞች በትናንሽ ጀልባዎች ወደ ብሪታንያ እንዳይመጡ የሚከለክል ሕግ የብሪታንያ ፓርላማ ካጸደቀ በኋላ ነው ሱናክ ይህን ያሉት።