1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አውሮጳውያን ቅኝ ገዢዎች አፍሪቃን ከ70 ዓመታት በላይ አስተዳድረዋል።

Tamirat Geletaሰኞ፣ መጋቢት 9 2016

አውሮጳውያን ቅኝ ገዢዎች አፍሪቃን ከ70 ዓመታት በላይ አስተዳድረዋል። በዚህ ጊዜ ታዲያ ማህበረሰቡ ከአንዱ ቦት ተነቅለው ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ መደረግ አልያም ለዘልአለሙ እንዳይመለሱ ማድረግ ፤ ይህ ብቻም ሳይሆን ማንነታቸውን እንዲያጡ እና እንዲጠፉ ተደርገዋል። በቅኝ ግዛት ዘመን ለየአካባቢው አዲስ ስም መሰየም ቀላል ይመስል ነበር። ነገር ግን እውነቱ እንደዚያ አልነበረም።

https://p.dw.com/p/4cWQr

 የጀርመን ቅኝ ግዛት አስከፊ ታሪክ ቅሪት ፤ ክፍል አምስት 

አውሮጳውያን ቅኝ ገዢዎች አፍሪቃን ከ70 ዓመታት በላይ አስተዳድረዋል። በዚህ ጊዜ ታዲያ ማህበረሰቡ ከአንዱ ቦት ተነቅለው ሌላ ቦታ እንዲሰፍሩ መደረግ አልያም ለዘልአለሙ እንዳይመለሱ ማድረግ ፤ ይህ ብቻም ሳይሆን ማንነታቸውን እንዲያጡ እና እንዲጠፉ ተደርገዋል። በቅኝ ግዛት ዘመን ለየአካባቢው አዲስ ስም መሰየም ቀላል ይመስል ነበር። ነገር ግን እውነቱ እንደዚያ አልነበረም። ቅኝ ገዢዎች የአፍሪቃን ምድር የራሳቸው ለማድረግ የመጨረሻ ማህተማቸው ነበርቅኝ ግዛትን መታገል የአፍሪካውያን የተቃውሞ ታሪክ ነው ።  የኪሊማንጃሮ ተራራ ለአካባቢው የቻጋ ምህበረሰብ የነበረው ባህላዊ ጠቀሜታ ሙሉ በሙሉ ችላ ተብሏል። ነገር ግን አውሮጳውያኑ አሳሾች በማህበረሰቡ ዘንድ እንደምልክት የሚታዩ ልዩ አካባቢዎችን እንደገና መሰየም የሚያመጣላቸውን ጠቀሜታ ጠንቅቀው ያውቃሉ ። በዚህም ራሳቸውን አዲሶቹ የአፍሪቃ ጌቶች እና ነባር አፍሪቃውያን ነዋሪዎችን ለማሰልጠን እንደመጡም ራሳቸውን ያቀርባሉ ። ከዚህ የተነሳ በአካባቢው ነዋሪዎች ይጠሩ የነበሩ መሰል አካባቢዎች ስሞች እንዳይጠሩ ብሎም በሂደት እንዲረሱ  አድርጓቸዋል።#የጀርመን ቅኝ ግዛት አስከፊ ታሪክ #Shadows of German colonialism

አዘጋጅ ካይ ኔቤ

ተርጓሚ እና ተራኪ ታምራት ዲንሳ