ኢትዮጵያ ካለፉት አራት ዓመታት ወዲህ ይህን መድሃኒት መጠቀም ማቆሟን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ገልፀዋል። ዲዲቲ መጠቀም እንዲቀር ለዉሳኔ ካደረሱ ምክንያቶች አንዱ የወባ ትንኝ መድሃኒቱን መቋቋም መጀመሯ ነዉ።
በየዓመቱ በጎሮጎሮሳዊዉ ቀን አቆጣጠር ሚያዚያ 22 ቀን ላይ ይታሰባል የመሬት ቀን። ይህ ከእምነት ጋ የማይገናኝ በዓል ሲከበርም 43ኛ ዓመቱን ይዟል። አነሳሱ ሰዎች ለአካባቢ ተፈጥሮ ትኩረት እንዲሰጡና ተፈጥሮን እንዲከባከቡ በሚል ነዉ።
የመሬት ሃብትን በአግባቡ ተጠቅሞ በምግብ እህል ራስን መቻል ከፍተኛዉ የአፍሪቃ ሀገሮች ፈተና እንደሆነ እየታየ ነዉ። በርካታ ሀገሮች የተፈጥሮ ሃብቶችን በጥንቃቄ ተጠቅመዉ ህዝባቸዉን ለመመገብ ጥረት ይዘዋል።
በበረሃ መስፋፋትና በድርቅ ምክንያት የሚከሰተዉ የመሬት ለምነት ማጣት በየዓመቱ ከእርሻ ምርት ከሚገኘዉ 349 ሚሊዮን ዩሮ እንደሚያሳጣ የዘርፉ ተመራማሪዎች ጥናት አመለከተ። በዚህ ምክንያትም ከስምንት መቶ ሚሊዮን በላይ ህዝብ ለከፋ የረሃብ አደጋ እንደሚጋለጥ ተነግሯል።
ባህላዊውን ህክምናን ከዘመናዊ ህክምና ጋር ማቀናጀቱ አሁንም አወዛጋቢ ሆኖ እንደቀጠለ ነው ። የኢትዮጵያ ባህላዊ መድሓኒት አዋቂዎች ማህበር ፣በአሁኑ ጊዜ ትክክለኛውንና ሃሰተኛውን የባህል መድኃኒት አዋቂ መለየቱ ደግሞ ሌላው አሰቸጋሪ ጉዳይ መሆኑም አስታውቋል ።
የዕለቱን ዝግጅት ለማዳመጥ 16:00 - 17:00 የሚለውን ማገናኛ ይጫኑ። የአንድ ሣምንቱ የስርጭት ኮሮጆም "ዝግጅት"ን በመጫን ሊገኝ ይችላል። የአማርኛ፣ የኪስዋሂሊ፣ የሀውሳ፣የእንግሊዝኛ፣ የፈረንሣይኛ እና የፖርቱጊዝኛ ቋንቋ ሥርጭትን በሚተላለፍበት ጊዜ በኢንተርኔት በInternet Explorer 8 በቀጥታ ማድመጥም ይቻላል።
በማድመጥ መማር እያዝናና መረጃ የሚሰጥ ዝግጅት ነው።
ግሎባል አይዲያስ