የኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት ተግባራዊነቱ
እሑድ፣ ታኅሣሥ 6 2006ማስታወቂያ
ሕገ-መንግሥቱ የተረቀቀና የፀደቀበት መንገድ ያኔም-አሁንም ቢያከራክርም በአብዛኞቹ አንቀፆቹ የተካተቱ ሐሳቦች በኢትዮጵያ ሠላማዊ ዲሞክራሲዊና ፍትሐዊ ሥርዓት ለመገንባት የግለሰቦችና የቡድናትን መብትና ነፃነት ለማስከበር እንደሚጠቅሙ ባለሙያዎች ያምናሉ።የሕገ-መንግሥቱ ገቢራዊነት ግን ብዙ አወዛጋቢ ነዉ።እንዲያዉም ተቃዋሚ ፖለቲከኞች የፕረስና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እንደሚሉት በሥልጣን ላይ ያለዉ መንግሥት የራሱን ሕገ-መንግሥት እየጣሰ በርካታ ደንቦችን ያወጣል፥ እርምጃዎችን ይወስዳልም።ውይይቱን ከድምፅ ዘገባው ያገኙታል።
ነጋሽ መሀመድ
ልደት አበበ