1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

ለትንበያ ያስቸገረው የብሪታኒያ ምርጫ

ረቡዕ፣ ሚያዝያ 28 2007

የነገው አጠቃላይ ምርጫ ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አስቸጋሪ ሆኗል ። በአሁኑ ምርጫ እስከዛሬ ብዙም ድጋፍ ያልነበራቸው ፓርቲዎች የተሻለ ድምጽ ሊያገኙ ይችላሉ ተብሎ ይጠበቃል ።

https://p.dw.com/p/1FL16
Großbritannien David Cameron Wahlkampf 2015
ምስል Reuters/N, Hall

ነገ በመላ ብሪታኒያ በሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ የሚሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ዛሬ የመጨረሻ የምርጫ ዘመቻቸውን አካሂደዋል ።ባለፉት 5 ሳምንታት በተካሄዱት የምርጫ ዘመቻዎች ከዋነኛዎቹ ተፎካካሪዎች ከወግ አጥባቂው ፓርቲ እጩ ዴቪድ ኬምረንም ሆነ ከሌበር ፓርቲው ተወዳዳሪ ኤድ ሚሊባንድ ማንኛቸው የመሪነቱን ቦታ ሊይዙ እንደሚችል ግልፅ አልነበረም ። በዚህ የተነሳም የነገው አጠቃላይ ምርጫ ውጤት ምን ሊሆን እንደሚችል ለመገመት አስቸጋሪ ሆኗል ። በአሁኑ ምርጫ እስከዛሬ ብዙም ድጋፍ ያልነበራቸው ፓርቲዎች የተሻለ ድምጽ ሊያገኙ ይችላሉ ተብሎ ይጠበቃል ።ስለ ነገው የብሪታኒያ አጠቃላይ ምርጫ የለንደኑን ዘጋቢያችንን ድል ነሳ ጌታነህን ስቱድዮ ከመግባቴ በፊት በስልክ አነጋግሬዋለሁ ።

ድል ነሳ ጌታነህ

ኂሩት መለሰ

ተክሌ የኋላ

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ

ተጨማሪ መረጃ ይፈልጉ